Showing posts with label ፬. ቤተ-አምልኮ. Show all posts
Showing posts with label ፬. ቤተ-አምልኮ. Show all posts

Tuesday, 4 November 2025

ብሔረ ብፁዓን


‎አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን

‎ባሕረ ጥበባት የሆነች ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን አስተምህሮዋ ሙሉ በሙሉ በመለኮታዊ መገለጥ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ በሥጋዊና በደማዊ የግል አስተሳሰብና ፍልስፍና ላይ የተመሠረተ አንድም አስምህሮ የላትም፡፡ ከልዑል እግዚአብሔር ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው ልጆቿም ቅድስናን ገንዘብ ያደረጉ ናቸው፡፡ ቅድስናንም ገንዘብ ማድረጋቸው ሰማያዊው ምሥጢር ፍንትው ብሎ እንዲታያቸው ምክንያት ሆኗቸዋል፡፡

‎ፈጣሬ ዓለማት ልዑል እግዚአብሔር አንድ ዓለም ብቻ ሳይሆን 20 የተለያዩ ዓለማትን እንደፈጠረ የምታውቅ ብቸኛዋ የእምነት ተቋም ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ብቻ ናት፡፡ ስነ ፍጥረትን እጅግ በሚገርም ሁኔታ ተንትኖ የሚያቀርበው መጽሐፈ አክሲማሮስም ሆነ ሌሎቹ ቤተክርስቲያን ድርሳናት እንደሚያስረዱት ከሆነ እግዚአብሔር 20 የተለያዩ ዓለማትን ፈጥሯል። እነዚህም፡- 5ቱ ዓለማተ መሬት፣ 4ቱ ዓለማተ ማይ፣ 2ቱ ዓለማተ ነፋስ እና 9ኙ ዓለማተ እሳት ናቸው፡፡

Thursday, 30 October 2025

ነገረ ማርያም

መግቢያ፡- 

ይህ የነገረ ማርያም ትምህርት ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ከፅንሰቷ ጀምሮ እስከ ዕርገቷያ ያለውን የሕይወቷን ታሪክ ብቻ የሚያጠና ሳይሆን ፣ስለ አምላክ እናትነቷ (እግዚአብሔር ወልድ ተወለደ፣ሰው  ሆነ ስንል እንዴት ሰዉ ሆነ የሚለዉን ጥያቄ ለመመለስ) ፣ ስለ ዘላለማዊ ድንግልናዋ፣ በነገረ ሥጋዌ (በነገረድ ድኅነት ትምህርት ዉስጥ ) ስላላት ድርሻ ፣ ስለ ንጽሕናዋ ፣ቅድስናዋ፣ስለተሰጣት ክብር ጨምሮ የሚያጠና የሚያካትት የሃይማኖት ትምህርት ክፍል ነው፡፡ ነገረ ማርያም የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን የነገረ ድኅነት  አስተምህሮ አካል ነዉ፡፡

መጽሃፉን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ 👇👇👇

https://drive.google.com/file/d/1KTISm0Nsu-1_xEm-PRKsyHHAwZhYEfI_/view?usp=drivesdk




Thursday, 23 October 2025

የ666 ሚስጥር እና ከኢሉሚናቲ ሚስጥራዊ ማህበረሰብ በስተጀርባ የተደበቀው እውነት

ምዕራፍ1፡ የ666 እና  የአውሬው ምንነት

📌 የ666 ትርጉም፡-

በመጀመሪያ ደረጃ፣ 666 ቁጥር ከክርስትና መጽሐፍ ቅዱስ የመጣ ነው። የዮሐንስ ራእይ 13:18 "ጥበብ ያለው ሰው አውሬውን ቁጥር ያስብ፤ ቁጥሩ ደግሞ የሰው ቁጥር ነውና፤ ቁጥሩም ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት (666) ነው።" በራእዩ ውስጥ፣ "አውሬ" የሚለው ቃል የሐሰት ነቢይ ወይም ፀረ-ክርስቶስ (AntiChrist) ማለት ነው። ስለዚህ 666 የፀረ-ክርስቶስ ምልክት ወይም "ቁጥር" ነው። ይህ ክፉ፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚቃረን ኃይልን ያመለክታል።

ከስሙ ትርጉም ስንነሳ፤ እነዚህ ሦስት ስድስቶች ምንድን ናቸው? በብዙ መልኩ ሊቃውንት አባቶቻችን ቢተረጉሙትም  ለግንዛቤ ያህል ሁለቱን ጠቅሼ አልፋለሁ።

✔ 1ኛ... 666 ማለት፤ የመጀመሪያው 6 የሚወክለው የሰው ልጅ የተፈጠረበትን ቀን ነው። ይህም ስድስተኛው ቀን ነው። ሁለተኛው 6 የሚወክለው የቀትር አጋንንት (ማለትም የአየር ላይ አጋንንት) ከሰማይ ወደ ምድር የተበተኑበትን ሰዓት ይወክላል።  ሦስተኛውና የመጨረሻው 6 ደግሞ የሚወክለው፤ መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት፣ ጠላት ዲያቢሎስ ድል የተነሳበት፣ ነፍሳት ከሲኦል የወጡበት ሰዓት ስለሆነ በዋናነት እነዚህን ሦስት ስድስቶችን የያዙትን ጊዜአት እንደሚቃወም ለመግለፅ ራሱን በሦስት ስድስቶች (666) ወከለ በማለት ሊቃውንት አባቶች ያመሰጥሩታል።

✔ 2ኛ.... 666 ምንድን ነው ለሚለው ደግሞ፤ አባቶቻችን በጥንት መፅሐፍቶች ላይ ከትበውልን እንዳለፉት፤ ሦስት ስድስቶች የሆኑበትን ምክንያት 'ሥላሴን እቃወማለሁ' ማለት ነው ይላሉ። እንዴት ቢሉ፤ ሥላሴ ማለት 'ሠለሰ' ከሚለው የግዕዝ ግስ የወጣ ሲሆን 'ሦስት አደረገ፣ ሦስት' የሚል ትርጉም አለው። የሥላሴ ሦስትነት ምን አይነት ሦስትነት ነው ቢሉ መልሱ ልዩ ሦስትነት ነው። የስድስቶች ብዛት (666) ሦስት የሆነበት ምክንያት አንድም የሥላሴን ልዩ ሦስትነት እቃወማለሁ ሲል ነው ይላሉ።

Saturday, 18 October 2025

ማኅሌተ ጽጌ፤ ምንጩ ትርጉሙና መልእክቱ


ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ኃይለ ቃልን ከትርጓሜ፣ ትርጓሜንከምሥጢር እንዲሁም ደግሞ ምሥጢርን ከዜማ ጋርአስተባብረውና አስማምተው የሚደርሱ ሊቃውንት ባለቤትናት፡፡ በ5ኛው መ.ክ.ዘመን የተነሣው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድአምስቱን ጸዋትወ ዜማ ሲደርስ በ14ኛው መ.ክ.ዘመንየተነሣው አባ ጊዮርጊስ ደግሞ ሰዓታትን ደርሷል፡፡ በዚሁ ዘመንአባ ጊዮርጊስ ጋር ጥልቅ መንፈሳዊ ፍቅር የነበረው አባ ጽጌድንግል “ማኅሌተ ጽጌ” የተባለውን ድርሰት ደርሷል፡፡ ማኅሌተጽጌ ግጥማዊ አካሔድ ያለው ድንቅ ኢትዮጵያዊ ድርሰት ነው፡፡ይህ ድርሰት በማንኛውም ጊዜ የሚጸለይ ቢሆንም በተለየ ሁኔታበቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውለው ከመስከረም 26 እስከኅዳር 5 ቀን ድረስ ባለው የእመቤታችን የቅድስት ድንግልማርያም የስደት ዘመን ነው፡፡ በዚህ ወቅት በየሳምንቱ እሑድሌሊት በሙሉ የእመቤታችንን ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ መሰደድናመንከራተት እያሰቡ የሚደረስ ምሥጋናና ጸሎት ነው፡፡

በሀገራችን የመስከረምና የጥቅምት ወራት የአበባ ወራት /ዘመነ ጽጌ/ ናቸው፡፡ ይህም ወቅት ተራሮች በአበባየሚያጌጡበትና ለዓይን ማራኪ የሚሆኑበት ጊዜ ነው፡፡በዚህም ዘመን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ስለልብስስ ስለምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴትእንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፡፡ አይደክሙም፣አይፈትሉም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩሁሉ ከእነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም፡፡ እግዚአብሔርን ዛሬያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህየሚያለብሰው ከሆነ እናንተ እምነት የጐደላችሁ እናንተንማይልቁን እንዴት እንግዲህ ምን እንበላለን ምንስ እንጠጣለን?ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ ...» /

Saturday, 4 October 2025

ደብረ ደደክን ፍለጋ‼️ ገነት ያለችብት ስፍራ 👉 ከኢትዮጵያ ጀርባ ምን መለኮታዊ ሚስጥር አለ?

 በቲና በቀለ


#ከአመታት_በፊት እንዲህ ሆነ... ከአንድ ወዳጄ ጋር ባህርዳር ጣና አካባቢ ተቀምጠን በብዙ ሀሳቦች ላይ እየተወያየን ባለንበት ሰአት እኛ ከተቀመጥንበት በስተቀኝ በኩል ጓደኛዬ የሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎችን ይመለከታል እንዳስታውላቸው ይነግረኛል።

ሴትና ወንድ በእድሜም ጠና ያሉ ነጮች ናቸው፤ ወደ ሰሜን ምዕራብ ጣና ሀይቅ አካባቢ ውድ፣ ዘመናዊ በግለሰብ ደረጃ ብዙም የማይገኘው መቅረጸ ትዕይንት Camera አቅርቦ የሚያሳይ telescope ከጀረባቸው እንዲሁም ትልቅዬ ቦርሳን አዝለው ወደ ሀይቁ አይናቸውን በሁለት አቅጣጫ እያመላለሱ በተደጋጋሚ ይመለከታሉ።


ለብዙ ደቂቃወች ይህንን የጠለቀ እይታ እና የሚጠቀሙትን ውድ ዘመናዊ Telescope ስመለከት እኒህ ሰው የመልካ ምድር አሳሾች ወይም የጥንት መዛግብት ተመራማሪወች ሊሆኑ እንደሚችሉ ገመትኩ።......

Thursday, 31 October 2024

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዘንድ ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ነው?

‎ኢየሱስ ክርስቶስ፦


‎ከሦስቱ አካላት አንዱ የሆነ፤ (ማቴ ፳፰፥፲፱)
‎ከአብ ጋር ዕሪና ያለው፤   (ዮሐ ፲፥፵)
‎ዓለም ሳይፈጠር የነበረ፤   (ዮሐ ፩፥፩)
‎ዓለምን የፈጠረ ፈጣሪ፤  (ዕብ  ፲፩፥፪)
‎በቅድምና ከአብ የተወለደ፤ (መዝ ፪፥፯)
‎ሥጋ እንደሚለብስ በራሱ የመሰከረ፤ (ዘፍ ፫፥፳፪)
‎ወደ ገነት ገብቶ አዳምን የፈለገ፤ (ዘፍ ፫፥፱)
‎በነቢያት አስቀድሞ የታወቀ፤ (ኢሳ ፵፪፥፩-፭)
‎አብ ልጄ ብሎ የጠራው፤ (ማቴ ፲፯፥፭)
‎ምሳሌ የተመሰለለት፤    (፩ኛ ቆሮ ፲፥፬)
‎ሱባዔ የተቆጠረለት፤  (ገላ ፬፥፬)
‎በብሥራተ መልአክ የተጸነሰ፤ (ሉቃ ፩፥፴፩)
‎ሥጋን የለበሰ (ማቴ ፩፥ ፳፫)
‎ቁራኝነትን ያጠፋ፤ (፩ኛ ቆሮ ፲፭፥፳፬)

Monday, 24 April 2023

ስለእመቤታችን ስዕለ አድኖ

 አንባቢያን ልታስተውሉት የሚገባው እጅግ በምስጢር ከተሞላው የእመቤታችን ስዕለ አድኖ እኔም እናንተም በጥቂቱ እናውቅ ዘንድ በማሳጠር በአጭር አማርኛ የፃፍኩት እና ሌሎች ትርጓሜዎችም ያሉት መሆኑን ልትረዱ ይገባል!! በተጨማሪ ቀስት ከቀስት ለይታችሁ ተመልከቱ!



#ሀ > አክሊለ ብርሃን ሲሆን ይህም በሁሉም ቅዱሳን አናት ላይ ተደርጎ የሚቀመጥ ሲሆን ቅዱስነታቸውን፤ መንፈስ ቅዱስ ያደረባቸው መሆኑን ያመለክታል!

#ለ > የእመቤታችን ከውስጥ የምትለብሰው ቀይ ልብስ ፤ አረጋዊ ስምዖን በነፍስሽ ሰይፍ ያልፋል እንዳላት ጌታን ከፀነሰች ጀምሮ ከእርሱ ጋርም የደረሰባትን ሀዘን፤ ጭንቁን፤ መከራዋን ሁሉ የሚያመለክት ሲሆን አንድም እሳተ መለኮትን በውስጧ የተሸከመች መሆኗን ያመለክታል!!

#ሐ > በእመቤታችን በስተ ቀኝ ትከሻዋ ላይ ያለው ኮከብ ጊዜ ወሊድ ድንግል መሆኗን ያመለክታል!

Tuesday, 1 March 2022

ቅዱስ ጊዎርጊስ

 


አንስጣስዮስ ከሮም ወደ ፍልስጤም በፈቃደ እግዚአብሔር ሄደ።በዚያም ከክቡራን መኳንንት፣ ከታላላቆች መሳፍንት መካከል አንዱ ነበር። ከፍልስጤም ዕጻ ከምትሆን ድያስ ከተባለች አገር ቴዎብስታ (አቅሌስያ) የምትባል ደግ ሚስት አገባ። የቴዎብስታ የስሟ ትርጓሜ ቤተ ክርስቲያን ማለት ነው። አቅሌስያም እንደ ስሟ የተቀደሰች፣ የተመሰገነች፣ የተባረከች፣ የተመረጠች በብርሃኑ ዓለምን ሁሉ ያበራውን የሰማዕታትን ኮከብ ይሸከም ዘንድ እግዚአብሔር ማህጸኗን የባረከላት ሴት ነበረች።እነዚህ ሁለት ደጋግ የእግዚአብሔር ሰዎችም ዘሮንቶስ (አንስጣስዮስ) እና ቴዎብስታ (አቅሌሲያ) በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ ተጋብተው በህይወታቸው እግዚአብሔርን የሚያስደስት ተግባር ይፈጽሙ ነበር። ጥር 20 ቀን 277 ዓ.ም በሀገረ ፍልስጤም ልዩ ስሟ ልዳ በተባለ ስፍራ ደም ግባቱ ያማረ፣ መልከ መልካም ሊቀ ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ወለዱ። በተጨማሪም ማርታና እስያ የሚባሉ ሁለት ሴቶች ልጆችን አፈሩ።

Wednesday, 23 February 2022

"ይህችን ዓመት ተወኝ!"


ከዓመት እስከ ዓመት - ፍሬን ሳላፈራ - ደረቅ እንደሆንኩኝ

በራድ ወይም ትኩስ - ሁለቱንም ሳልሆን - እንዲያው ለብ እንዳልኩኝ

አለሁኝ በቤትህ - ለሙን መሬትህን - እያጎሳቆልኩኝ

አውቃለሁ አምላኬ - ፍሬዬን ለመልቀም - እንዳመላለስኩህ

ዛሬም ሳላፈራ - እሾህን አብቅዬ - ደርቄ ጠበቅሁህ

ያልተደረገልኝ - ያላፈሰሰክብኝ - ያልሰጠኸኝ የለም

ነገር ግን ይህ ሁሉ - አላርምህ አለኝ - አልለየኝም ከዓለም

የማትሰለቸኝ ሆይ - ተነሥቼ እስክቆም - እባክህ ታገሠኝ

የእኔን ክፋት ተወው - መልአክህን ሰምተህ - ይህችን ዓመት ተወኝ!

Sunday, 13 February 2022

ፆመ ነነዌ

ነነዌ Nineveh

ነነዌ የአሦራውን ጥንታዊ ዋና  ከተማ ስትሆን በላዕላይ መስጴጦምያ በአሁኑ አጠራር በሰሜናዊ ኢራቅ የምትገኝ ከተማ ስትሆን ከተማዋን ሶርያ፣ ቱርክ እና ኢራን ያዋስኗታል፡፡

ነነዌ የአሦራውያን ከተማ

ነነዌ በጤግሮስ ወንዝ ዳር በ4000 ቅ.ል.ክ. ገደማ በኩሽ ልጅ ናምሩድ የተቆረቆረች ከተማ  ከተማ ናት (ዘፍ.10፡11-12)።  ነነዌ  የአሦራውያን ዋና ከተማ እና መናገሻ የሆነችው ግን በ1400 ቅ.ል.ክ. ነው  (2ነገ.19፡36)፡፡ አሦር የተባለው የሴም ሁለተኛ ልጅ (ዘፍ.10፥22)  አሦራውያን ለተባሉት ሕዝቦች የመጀመሪያ አባት ነበር። ሀገራቸው በላይኛው መስጴጦምያ ነው። ነነዌም ዋና ከተማቸው ነበረች። 

Saturday, 12 February 2022

የ"ቶ" ፊደል ምስጢር እና ታሪክ

የ "ቶ" ፊደል የተፈጠረዉ አለም ሲፈጠር ነዉ። የሰዉ ልጅ የተፈጠረዉ በ"ቶ" ቀመር መሆኑ አጀብ ያስብላል። በግዕዝ የፊደል ስርአት መሰረት (ተ ቱ ቲ ታ ቴ ት ቶ) "ቶ" ሰባተኛዋ ፊደል ነች። ሰባት ቁጥር ብዙ ትርጉምና ምስጢር አለው፡፡ ሰባት ቁጥር በቤተክርስትያን ፍፁምነትን ይወክላል።

ለምሳሌ:-

📌7ኛው ዙፋን የጌታ እንደሆነ ፣

📌7ኛው ቀን ሰንበት እንደሆነች ፣

📌7ቱ ሰማያት

📌7ቱ ምስጢራተ ቤተክርስትያን

📌7ቱ የመላእክት አለቆች 

ከ"ተ" የፊደል ዘር "ቶ"ን ስንመለከት መልክአ ፊደሉ ሰው መሳይ ሲሆን ትርጓሜው ደግሞ አምላክ ሰው መሆኑን እናምናለን ማለት ነው። 7ቱ ባህርያትን መዋሐዱን ያመለክታል። የሰዉ ልጅ የተፈጠረዉ በ"ቶ" ቀመር መሆኑም አጀብ ያስብላል። 

Friday, 28 January 2022

ጥር 21 የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት

ጥር 21 በዓለ አስተርእዮ (የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት)


ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በስድሳ አራት አመቷ ከሞት ወደ ሕይወት ከመከራ ወደ ደስታ የተሸጋገረችበት ዕለት ነው፡፡
ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ያሬድም “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” ትርጉሙ ሞት ለማናኛቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል፡፡ በማለት አደነቀ፡፡ በመሆኑም በዓሉ የወላዲተ አምላክ በዓለ ዕረፍት ከመሆኑ የተነሳ ታላቅ በረከት የሚያስገኝ ስለሆነ በየዓመቱ ይከበራል፡፡

Wednesday, 19 January 2022

ቃና ዘገሊላ



 ‹‹ቃና ዘገሊላ›› ምንድነው?

ቃና ዘገሊላ በቀጥታ ትርጉም የገሊላዋ ቃና ማለት ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ በጥምቀት በዓል ማግስት(ጥር 12) ቀን የቃና ዘገሊላ በዓል ይከበራል፡፡ ይህ በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በድምቀት የሚከበር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዳራ ያለው በዓል ነው፡፡ በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ ያገኘው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ሀገር ክፍል በምትሆን ቃና በተባለችው ቦታ በፈፀመው ተአምር መነሻነት ነው፡፡ የቃና ዘገሊላ ጥንተ ነገሩ ወይም ታሪኩ የተፈፀመው የካቲት 23 ቀን ነው፡፡ ነገር ግን አባቶቻችን የውኃን በዓል ከውኃ በዓል ጋር ለማክበር ብለው የየካቲቱን በዓል ወደ ጥር 12 አምጥተውታል፡፡ ይህም ውኃ ወደ ወይን የተለወጠበትን በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ለማስተሣሠር ለማስኬድ ነው፡፡ በመሆኑም የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር 12 ቀን ይከበራል፡፡

Tuesday, 18 January 2022

ገሀድ፣ ከተራ እና የጥምቀት በኢትዮጵያ


═════ ❁ ═════

ገሀድ :

➢. ገሃድ የቃሉ ትርጉም መገለጥ መታየት ነው፡፡ በጥምቀት መገለጥ መባሉ ሰው የሆነው አምላክ በዓለም ሲኖር እስከ 30 ዓመት እድሜው ድረስ ሰዎችን ለማዳን የመጣ መሲህ ሰው የሆነበት፣ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ መሆኑን ሳያውቁ ከኖሩ በኃላ በ 30 ዓመት እድሜው በባሕረ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሲጠመቅ አብ በደመና ሆኖ ‹‹የምወደው ልጄ ይህ ነው›› በማለቱ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በራሱ ላይ ሲያርፍ በመታየቱ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ይሰቀላል ይሞታል ይነሳል ብለው የተናገሩለት መሲሕ እርሱ መሆኑ ተገልጦአልና እንዲሁም ሦስቱ አካላት በአንድ ጊዜ ታይተዋልና ምስጢረ ሥላሴ የተገለጠለት በመሆኑ ገሃድ ይባላል፡፡(ማቴ 3፡13-17)

ጥምቀት

ጥምቀት የሚለው ቃል “አጥመቀ” (አጠመቀ) ከሚለው የግእዝ ግሥ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙም በተከማቸ ውሃ ውስጥ መነከር፡ መዘፈቅ፡ ገብቶ መውጣት ማለት ነው። ምስጢረ ጥምቀት በምስጢራዊ (በሃይማኖታዊ) ፍቺው በተጸለየበት ውሃ (ማየ ኅይወት) ውስጥ በሥላሴ (በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ) ስም ሦስት ጊዜ ብቅ ጥልቅ ብሎ የመውጣት ሂደት ነው (ማቴ 28፡19)። ጥምቀት “የክርስትና መግቢያ በር” ናት፡፡ ምክንያቱም ከሌሎች ምስጢራት ስለሚቀድምና ለእነርሱም መፈጸም ቅድመ ሁኔታ ስለሆነ ነው፡፡ ጥምቀት ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማኅፀነ ዮርዳኖስ ተወልደን የሥላሴን ልጅነት የምናገኝበት (ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና) ምሥጢር ነው። ሰው ከሌሎች ምስጢራተ ቤተክርስቲያን ለመካፈል አስቀድሞ መጠመቅና ከማኅበረ ክርስቲያን መደመር አለበት፡፡ ስለዚህም ምስጢረ ጥምቀት ከአምስቱ አዕማደ ምስጢራት እንዲሁም ከሰባቱ ምስጢራተ ቤተክርስቲያን አንዱ ነው፡፡ የእምነታችን መሠረትም፣ የጸጋ ልጅነት የሚገኝበትም ምስጢር ነውና ከሁለቱም ይመደባል፡፡

Thursday, 6 January 2022

ልደተ ክርስቶስ


 ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ልደታት አሉት

ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሁለት ልደታት እንዳሉት ታምናለች ታሳምናለች፤ እነዚሁ ቀዳማዊ ልደትና ደኃራዊ ልደት ሲባሉ፤ ይኸውም ወልድ (ቃል) ቅድመ ዓለም ከአብ ያለ እናት ድኅረ ዓለም ከእመቤታችን ያለ አባት የተወለደው ልደት ነው፡፡ “ለእግዚአብሔር ልጅ ሁለት ልደታት እንዳሉት ልናምን ይገባናል፡፡ መጀመሪያ ከዘመን ሁሉ በፊት ከእግዚአብሔር አብ መወለዱ ነው፡፡ ዳግመኛም በኋላኛው ዘመን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደው መወለዱ ነው፡፡” ሲል ሊቁ አስረድቷል፡፡ (ሃይማኖተ አበው ባስልዮስ ዘቂሳርያ)

Monday, 6 December 2021

ሰብአ ሰገል

የሰብአ ሰገል ምንነት፥ ታሪክ፥ ኮከቡ፥ ጉዟቸው፥ በስተመጨረሻው መሰወራቸው

አባታችን አዳም በዕለተ አርብ በነግህ ከተፈጠረ በኋላ እናታችን ሔዋን በሳምንቱ አርብ በዘመናችን አነጋገር 3 ሰዓት ላይ ከግራ ጎኑ ተፈጠረች። በገነትም 7 ዓመት ከ3 ወር ከ 17 ዕለታት ካሳለፉ በኋላ ሕግን ተላልፈው እፀ በለስን በመብላታቸው ከገነት ተባረሩ። በዚህ ግዜ አምላካችን እግዚአብሔር ለአዳም የተስፋ ቃል ሰጠው፤ እርሱም ከልጅ ልጅህ ተወልጀ ከ5 ቀን ከመንፈቅ በኋላ አድንሃለሁ የሚል ቃል ነበረ። ይህ የተስፋ ቃልና ከመላእክት ለአዳም የተሰጡትን ስጦታዎች አዳምና የልጅ ልጆቹ ሲቀባበሉት ቆይቶ ከካሕኑ መልከጼዴቅ እጅ ላይ ደረሰ። ከመልከጼዴቅ አንዳንዶቹ ለአብርሃም ተሰጠ ሲሉ አንዳንዶቹ ደግሞ ለኢት-ኤል ተሰጠ ይላሉ። 

Saturday, 6 March 2021

አምሓራ ሳይንት አስት ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ቤተክርስቲያን



 ኑ የበረከት ስራ እንስራ

ቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ዘብዴዎስ፣ ወልደ ነጎድጓድ፣ ፍቁረ እግዚእ፣ ነባቤ መለኮት(ታኦሎጎስ)፣ ቁጽረ ገጽ በመባል የሚታወቀው ወንጌላዊው ቅዱስ ዩሐንስ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ ሲሆን የመጀመሪያው ወጣት የመጨረሻው ሽማግሌ ሐዋርያ እሱ ነበር፡፡ 

ቅዱስ ዩሐንስ የተወለደው በገሊላ አውራጀ በቤተ ሳይዳ ነው፣ አባቱ ዘብዴዎስ ይባላል፡፡ ቅዱስ ዩሐንስ ገና በወጣትነቱ ዘመን ከወንድሙ ከያዕቆብ ጋር ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮ የጌታውን እግር ተከትሎ አድጓል፡፡ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ የጌታ ደቀ መዝሙር ከመሆኑ በፊት የመጥምቀ መለኮት የቅዱስ ዮሐንስ ደቀ መዝሙር ከነበሩት ደቀ መዛሙርት አንዱ ነው፡፡

Friday, 26 February 2021

Tedbabe Mariam Negist (The Queen of the Monasteries)

 

Tedbabe Mariam Negist (The Queen of the Monasteries)







Tedbabe Mariam, one of the ancient monasteries of the Ethiopian Orthodox Tewahido church, is found 600 km north of Addis Ababa in south Wollo Diocese west of Dessie Town in Amhara Sayint Woreda. The distance from Addis Ababa to Dessie Town is 400 km and from Dessie to Tedbabe Mariam 200 Km, covering a total of 600 km.

Sunday, 21 February 2021

ነነዌ

👉Neway Kassahu's View  (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)

ነነዌ

ወቅቱ በቤተክርስቲያናችንን አስተምህሮ በቀናት አነስተኛ የሆነችው ጾም፤ ጾመ ነነዌን የምንጾምበት ወቅት ነው፡፡ ቀኑ እንጂ ተግባሩና ትምህርቱ ግን ሰፊ ነው። ነነዌን ብዙ ጊዜ ከምንሰማውና ካስተማርነው በላይ ትልቅ ምስጢራዊና ታሪካዊ ከተማ ናት፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያና ነነዌን የምናነጻጽርበት ብዙ ገጽታ አለን፡፡

ነነዌ የአሦራውን ጥንታዊ ከተማ ስትሆን በላዕላይ መስጴጦምያ በአሁኑ አጠራር በሰሜናዊ ኢራቅ የምትገኝ ከተማ ናት፡፡ ከተማዋን ሶርያ ቱርክ ኢራን ያዋስኗታል፡፡

ከክርስቶስ ልደት በፊት በ 1800 ዓ.ዓ በኩሽ ልጅ ናምሩድ የተቆረቆረች ከተማ እንደሆነች መጽሐፍ ቅዱስ ይነግረናል፡፡ ዘፍ. 10፣ 11

በወቅቱ በአሦራውያን ግዛት ትልቋ የዓለም ከተማ ስትሆን በወቅቱ ታላቅ የሃይማኖት መዲና እንዲሁም የአሶራውያን አማልክት (ኬሽታር) ማማለኪ ስፍራ ተገንብቶባትም ነበር፡፡ ከተማዋ በተደጋጋሚ መሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ሲገጥማት የማምለኪያ ስፍራው ቢወድምም ከተማዋ እንደገና በ2260 ዓ.ዓ አካዲን በተባለው ንጉስ በድጋሚ ታንጻለች፡፡

ነነዌ በመጀመሪያ ስሟ የተጠቀሰው በዘፍጥረት 10፡11 ላይ ሲሆን የአሦር ግዛት ዋና ከተማ ነበረች፡፡ በንጉሡ ሕዝቅያስ ዘመን የይሁዳ ነቢይ የነበረው ኢሳይያስ የኖረባት፤ ሰናክሬም በ705 - 681 ዓዓ የገዛት፤ በኋላም በሁለት ልጆቹ አድራማሌቅና ሶርሶር በተባሉ ልጆቹ የተገደለባት ከተማ ናት፡፡ ኢሳ 37፡37-38

ነነዌ በአሁኑ አጠራር በሰሜናዊ ኢራቅ ከተማ ሞሱል (Mosul) በሚባል ስም ትጠራለች፡፡ በወቅቱ መቶ ሃያ ሺኽ ሰው ያኽል ይኖርባት የነበረ ሲሆን ከተማዋን ትንንሾቹን መንደሮች ጨምሮ ዞሮ ለመጨረስ ሶስት ቀን ይፈጃል።

ነነዌ በበደል ምክንያት እግዚብሔር ተቆጥቶ ሊያጠፋት ይኽንንም እንዲውቁ ዮናስን እንዲያስተምር አዘዘው፡፡ ሕዝቧ ሩህሩህ ስለነበር ከንጉሡ እስከ ሕዝቡ ሕጻናት እንስሳት ሳይቀሩ የእግዚአብሔርን ፊት ፈለጉ፣ ንሰሐ ገቡ እግዚአብሔርም ራራላቸው ይቅርም አላቸው፡፡ ነቢዩ ዮናስና ናሆም የነበረውን ታሪክ ጽፈው አቆዩልን፡፡ ነቢዩ ዮናስና ነቢዩ ዳንኤል መቃብር በዚያ የነበረ ሲሆን በአክራሪው እስልምና ISIS ሰራዊት ፈራርሷል፡፡