ከአምሐራ ሳይንት ወረዳ አጅባር ከተማ ወደ ርዕስ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም እየተሰራ ያለው መንገድ ስራ 90 በመቶ የሚሆነው የአፈር ጠረጋና ምንጣሮ ስራ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡
የአጅባር ተድባበ ማርያም መንገድ ስራ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ዑመር እንደገለጹት ከአጅባር ተድባበ ማርያም 30ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የአጅባር ተድባበ ማርያም መንገድ ስራ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በመሰራት ላይ እንደሆነ ገልጸው አስካሁን በተሰራው ስራ 23 ነጥብ 17 ኪ.ሜትር የሚሆነው መንገድ የአፈር ጠረጋና የምንጣሮ ሥራ ተሰርቶለታል ፡፡

