Showing posts with label ፫. ነጻ ሃሳብ. Show all posts
Showing posts with label ፫. ነጻ ሃሳብ. Show all posts

Saturday, 6 February 2021

ያላለቀው ልማታችን

 


ከአምሐራ ሳይንት ወረዳ አጅባር ከተማ ወደ ርዕስ አድባራት ወገዳማት ተድባበ ማርያም እየተሰራ ያለው መንገድ ስራ 90 በመቶ የሚሆነው የአፈር ጠረጋና ምንጣሮ ስራ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የአጅባር ተድባበ ማርያም መንገድ ስራ ፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ዑመር እንደገለጹት ከአጅባር ተድባበ ማርያም 30ኪ.ሜ ርዝመት ያለው የአጅባር ተድባበ ማርያም መንገድ ስራ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በመሰራት ላይ እንደሆነ ገልጸው አስካሁን በተሰራው ስራ 23 ነጥብ 17 ኪ.ሜትር የሚሆነው መንገድ የአፈር ጠረጋና የምንጣሮ ሥራ ተሰርቶለታል ፡፡

Wednesday, 3 February 2021

በጠያቂ እጦት ስትሰቃይ የኖረች አምሓራ ሳይንት

 

አምሓራ ሳይንት ለብዙ ዓመታት “ወንዝ የሚሻግራት” መሪ አጥታ ቆይታለች።  የአመራር ድክመቶች ሁሉ ምንጭ የመሪ ጉድለቶች ብቻ የሆነ አድርገን መውሰድ ይቀለናል። እኛ ተከታዮች ወይም ተመሪዎች (followers) ከመሪ ያላነሰ ተጠያቂነት አለብን። መሪዎቻችን ለአመራር ስኬት ብቸኛ ተወዳሽ መሆን እንደሌለባቸው ሁሉ ለአመራር ጉድለት ብቸኛ ተጠያቂ መሆን የለባቸውም። የመሪው ጉድለት መኖሩ ብናረጋግጥ እንኳን መሪው ብቸኛ ተጠያቂ ላይሆን ይችላል። ለአምሓራ ሳይንት ኋላቀር እድገት መሪና ተመሪውም ናቸው።