1. ንስሮች በከፍታ ለብቻቸው ይበራሉ፦ ንስር ፈፅሞ ከጥንብ አንሳ፣ ቁራና መሰል ትናንሽ አእዋፍት ጋር አብሮ አይበርም።📌 ንስርን በተፈጥሮ ከሚገዳደሩት የወፍ ዝርያዎች መካከል አንዱና ዋነኛ የሆነው ቁራ ነው። ቁራ በንስሩ ጀርባ ላይ በመፈናጠጥ የንስሩን አንገቱን እና ጀርባውን መንከስ ይጀምራል። በዚህን ጊዜ ንስሩ ለመከላከል ወይም ከላዩ ላይ ለማስወገድ የሚያደርገው አንዳችም ዓይነት ምላሽ አይኖርም። ጸብ ውስጥም አይገባም፣ ግጭትም አይፈጥርም።
ከቁራው ጋር እየታገለ ምንም ዓይነት ጊዜና ጉልበትንም አያባክንም። ነገር ግን አንድ ነገር ያደርጋል። ይህም ንስሩ ረዣዥም ክንፎቹን በመዘርጋት ከፍ ወዳለው ወደ ሰማየ ሰማያት መወንጨፍ ይጀምራል።
ከፍታው በጨመረ ቁጥር ቁራው አየር ንብረቱን መቋቋም ስለማይችል መተንፈስ አስቸጋሪ ይሆንበታል። በስተመጨረሻም በኦክስጂን እጥረት ምክንያት ቁራው ከጀርባው ላይ ይወድቃል። ከቁራዎች ጋር ጊዜያችሁን አታባክኑ።
ቀጥታ ወደ ከፍታ ውሰዷቸው። የዚያን ጊዜ መተንፈስ ስለማይችሉ አቅም በማጣት ተሸንፈው ይወድቃሉ። ግዜያችሁንና ጉልበታችሁን ከደካሞች ጋር በመላፋት አታባክኑ። ከፍታን ምረጡ!! እናንተ ከፍ ስትሉ ራሳቸው ይወድቃሉ እንጅ እነሱን ለመጣል ምንም ጉልበት አታባክኑ!!!


