Thursday, 31 October 2024

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ዘንድ ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ነው?

‎ኢየሱስ ክርስቶስ፦


‎ከሦስቱ አካላት አንዱ የሆነ፤ (ማቴ ፳፰፥፲፱)
‎ከአብ ጋር ዕሪና ያለው፤   (ዮሐ ፲፥፵)
‎ዓለም ሳይፈጠር የነበረ፤   (ዮሐ ፩፥፩)
‎ዓለምን የፈጠረ ፈጣሪ፤  (ዕብ  ፲፩፥፪)
‎በቅድምና ከአብ የተወለደ፤ (መዝ ፪፥፯)
‎ሥጋ እንደሚለብስ በራሱ የመሰከረ፤ (ዘፍ ፫፥፳፪)
‎ወደ ገነት ገብቶ አዳምን የፈለገ፤ (ዘፍ ፫፥፱)
‎በነቢያት አስቀድሞ የታወቀ፤ (ኢሳ ፵፪፥፩-፭)
‎አብ ልጄ ብሎ የጠራው፤ (ማቴ ፲፯፥፭)
‎ምሳሌ የተመሰለለት፤    (፩ኛ ቆሮ ፲፥፬)
‎ሱባዔ የተቆጠረለት፤  (ገላ ፬፥፬)
‎በብሥራተ መልአክ የተጸነሰ፤ (ሉቃ ፩፥፴፩)
‎ሥጋን የለበሰ (ማቴ ፩፥ ፳፫)
‎ቁራኝነትን ያጠፋ፤ (፩ኛ ቆሮ ፲፭፥፳፬)


‎በማሕጸን ጽንስን ያዘለለ፤ (ሉቃ ፩፥፵፩)
‎መላእክት የዘመሩለት፤  (ራእ ፬፥፰)
‎ተጸንሶ ሳል በሰማይም ያለ፤ (ሉቃ ፪፥፲፬)
‎በሕቱም ድንግልና የተወለደ ፤ (ማቴ ፩፥፳፫)
‎ያለ አባት ከሴት ብቻ የተወለደ፤ (ገላ፥ ፬፥፬)
‎አለቅነት በጫንቃው ላይ ያለ፤ (ኢሳ ፱፥፮)
‎ከሁለት አካል አንድ አካል የሆነ፤ (ዮሐ ፩፥፲፬)
‎ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ የሆነ፤ (ዮሐ ፪፥፲፱)
‎ንጉሥ ሆኖ የተወለደ፤    (ማቴ ፪፥፩-፪)
‎ለቤዛነት የተሰደደ፤ (ማቴ ፪፥፲፬-፲፭)
‎መምህር ሆኖ ሳለ ለመማር የሚሻ፤ (ሉቃ ፪፥፵፮)
‎በዮሐንስ እጅ የተጠመቀ፤ (ዮሐ ፫፥፲፭)
‎ላመኑት የዘላለም ሕይወትን የሚያድል፤ (፫፥፴፮)
‎የአብ ኃይሉና ቀኙ የሆነ፤ (፪ኛ ጤሞ ፫፥፭)
‎ጥምቀትን መዳኛ ያደረገ (ማር ፲፮፥፲፮)
‎ወንጌልን የሠራ፤ (ዮሐ ፩፥፲፯)
‎አዲስ ቃል ኪዳን የገባ፤ (ማቴ ፳፮፥፳፮)
‎የዓለሙን ኃጢአት የሚያስተሠርይ በግ፤ (ዮሐ ፩፥፳፱)
‎መጾምን ያስተማረ፤ (ማቴ ፬፥፪)
‎ፍቅርን የሰበከ፤ (ዮሐ ፲፭፥፲፫)
‎ከሙታን መካከል ተለይቶ የተነሣ፤ (ማቴ ፳፰፥፮)
‎ኦሪትን የፈጸመ፤ (ማቴ ፭፥፳፩-፵፰)
‎ከአብርሃም በፊት የነበረ፤ (ዮሐ ፰፥፶፰)
‎አልፋና ዖሜጋ የሆነ፤ (ራእ፩፥፲፯)
‎ምሕረቱ እጅግ የበዛ፤ (ዮሐ ፰፥፲፩)
‎ሐዋርያትን የጠራ፤ (ማቴ ፭፥፲፱-፳፩)
‎ሥጋውንና ደሙን የሰጠ፤ (ማቴ ፳፮፥፳፮)
‎ዓርአያነትን የሰጠ፤ (፲፫፥፲፭)
‎አዳኝ ሆኖ የተገለጠ፤ (ሉቃ ፱፥፶፮)
‎ለአዳም ቤዛ የሆነ፤ (ኤፌ ፩፥፯)
‎ይቅርታን ያስተማረ፤ (ሉቃ ፲፯፥፬)
‎ገነትን በደሙ የከፈተ፤ (ማቴ ፳፭፥፴፭)
‎፮ቱ ትዕዛዛተ ወንጌልን የነገረ፤ (ማቴ ፳፭፥
‎ሞትን ያሸነፈ፤ (፩ኛ ቆሮ ፲፭፥፶፬)
‎በመላእክት የተመሰገነ፤ (ማቴ ፬፥፲፩)
‎በሐዋርያት የተሰበከ፤ (ሐዋ ፪፥ ፳፪)
‎ፍርድ ሁሉ ለእርሱ የሆነ፤ (ዮሐ ፭፥፳፯)
‎ሊቀ ካህን ሆኖ የተገለጠ፤ ( ዕብ፯፥፳፮)
‎አምላክነት ገንዘቡ የሆነ፤ (ሮሜ ፱፥፭)
‎በሰውነቱ የሚራብ፤ (ማር ፲፩፥፲፪)
‎በአምላክነቱ የሚያጠግብ፤ (ሉቃ ፱፥፲፯)
‎ሊያገለግል የመጣ፤ (ማቴ ፳፥፳፰)
‎ሕይወትና ትንሣኤ ተብሎ የሚጠራ፤ (ዮሐ ፲፩፥፳፭)
‎እውነተኛ የበጎች ጠባቂ፤ ( ዮሐ ፲፥፲፩)
‎የቤተ ክርሰቲያናችን ራስ፤ (ኤፌ ፬፥፲፭)
‎ብርሃነ መለኮቱን የገለጠ፤ (፪ኛ ጴጥ ፩፥፲፮-፲፱)
‎ሙሴና ኤልያስን ያነጋገረ፤ (ማር ፱፥፬)
‎ለሙሽራይቱ ሙሽራ የሆነ፤ (ዮሐ ፫፥፳፱)
‎ዳግም ለመምጣት ቀጠሮ የያዘ፤ (ራእ ፳፪፥፲፪)
‎ትንቢተ ነቢያትን የፈጸመ፤ (ማቴ ፩፥፳፫)
‎የነቢያት አለቃቸው፤ (ሉቃ ፯፥፲፮)
‎የታመነ ምስክር፤  (ማቴ ፲፤፴፪)
‎ከአባቱ የሰማውን የሚናገር፤ (ዮሐ ፲፭፥፲፭)
‎አንድ ጊዜ ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ የገባ፤ (ዕብ ፱፥፲፪)
‎ገዳማዊ ሕይወትን የጀመረ፤ (ማቴ ፬፥፩)
‎ተባሕትዎን የወጠነ፤ (ማቴ ፰፥፳)
‎ጋብቻን ተገኝቶ የባረከ (ዮሐ ፪፥፪)
‎እናቱን  እነኋት ብሎ የሰጠ፤ (ዮሐ ፲፱፥፳፯)
‎የመስቀል ሞትን የሞተ፤ (ፊል ፪፥፰)
‎በብዙ ወገን የተገፋ፤ (ዮሐ ፭፥፲፮)
‎ደዌአችንን የተሸከመ፤  (ኢሳ ፶፫፥፬)
‎ነፍሱን ስለ እኛ የተወ፤ (ዮሐ፲፱፥፴)
‎ቅዱሳንን አብዝቶ የሚወድ፤ (ማቴ ፲፥፵)
‎በክብር ወደ ሰማይ ያረገ፤ (ሐዋ ፩፥፱)
‎ለነፍሳት ግዕዛንን የሰበከ፤ (፩ኛ ጴጥ ፫፤፲፱)
‎ለደካሞች ማረፊያ የሆነ፤  (ማቴ ፲፩፥፳፰)
‎በግርማ መለኮት የሚመጣ፤ (መዝ ፶፥፫)
‎ሙታንን የሚያስነሣ፤  (ዮሐ ፮፥፵፬)
‎የጌቶች ጌታ የሆነ፤ (ሮሜ ፲፥፲፪)
‎ከእውነቸኛ ብርሃን የተገኘ ብርሃን፤ (ዮሐ ፰፥፲፪)
‎ፈራጅነት ገንዘቡ  የሆነ አምላክ ነው! (ራእ፳፪፥፲፪)

‎እንዲህ እናምናለን እንዲህም እንታመናለን!

No comments: