ነነዌ Nineveh
ነነዌ የአሦራውን ጥንታዊ ዋና ከተማ ስትሆን በላዕላይ መስጴጦምያ በአሁኑ አጠራር በሰሜናዊ ኢራቅ የምትገኝ ከተማ ስትሆን ከተማዋን ሶርያ፣ ቱርክ እና ኢራን ያዋስኗታል፡፡
| ነነዌ የአሦራውያን ከተማ |
ነነዌ Nineveh
ነነዌ የአሦራውን ጥንታዊ ዋና ከተማ ስትሆን በላዕላይ መስጴጦምያ በአሁኑ አጠራር በሰሜናዊ ኢራቅ የምትገኝ ከተማ ስትሆን ከተማዋን ሶርያ፣ ቱርክ እና ኢራን ያዋስኗታል፡፡
| ነነዌ የአሦራውያን ከተማ |
📌7ኛው ዙፋን የጌታ እንደሆነ ፣
📌7ኛው ቀን ሰንበት እንደሆነች ፣
📌7ቱ ሰማያት
📌7ቱ ምስጢራተ ቤተክርስትያን
📌7ቱ የመላእክት አለቆች
ከ"ተ" የፊደል ዘር "ቶ"ን ስንመለከት መልክአ ፊደሉ ሰው መሳይ ሲሆን ትርጓሜው ደግሞ አምላክ ሰው መሆኑን እናምናለን ማለት ነው። 7ቱ ባህርያትን መዋሐዱን ያመለክታል። የሰዉ ልጅ የተፈጠረዉ በ"ቶ" ቀመር መሆኑም አጀብ ያስብላል።
ሚካኤል “አባ ሻንቆ” photo credit ሽፍታ |
በዛሬዋ ዕለት ጥር 27/1842 ዓ.ም ራስ ሚካኤል “አባ ሻንቆ” ከዛሬዋ ደሴ ላኮመልዛ በፊት ደግሞ ወይራ አምባ ከሰሜኗ የፍቅር ከተማ ክፍለ ሀገር ተንታ ተወለዱ።
ደሴ እንኳን ለሀገሬ ሰው ይቅርና በ7ኛው ክፍለ ዘመን ከአርመን ተሰደው ለመጡ ክርስቲያኖች መጠጊያ፤ ሰው እምነቱ እርስ በእርስ የማይባላባት፤ ሙስሊም ክርስቲያኑ የሚለው የወግ ማዕረግ በተግባር የሚታይባት የፍቅር ተምሳሌት ከተማ፤ እስላም ክርስቲያኑ፣ በረኸኛው ከደገኛው፣ ብሔረሰብ ሕዝቡ፣ ተፈጠሮና ሰው… ሁሉም በፍቅር የሚኖሩባት ምድር ደሴ።
| ጥር 21 በዓለ አስተርእዮ (የእመቤታችን በዓለ ዕረፍት) |
ወላዲተ አምላክ ምንም እንኳን የአምላክ እናት ብትሆንም ሞተ ሥጋ ለሁሉም ዕጣ ፈንታ በመሆኑ በስድሳ አራት አመቷ ከሞት ወደ ሕይወት ከመከራ ወደ ደስታ የተሸጋገረችበት ዕለት ነው፡፡
ታላቁ የቤተክርስቲያን አባት ቅዱስ ያሬድም “ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ” ትርጉሙ ሞት ለማናኛቸውም ሰው ሁሉ የተገባ ነው የማርያም ሞት ግን ሁሉን ያስደንቃል፡፡ በማለት አደነቀ፡፡ በመሆኑም በዓሉ የወላዲተ አምላክ በዓለ ዕረፍት ከመሆኑ የተነሳ ታላቅ በረከት የሚያስገኝ ስለሆነ በየዓመቱ ይከበራል፡፡
‹‹ቃና ዘገሊላ›› ምንድነው?
ቃና ዘገሊላ በቀጥታ ትርጉም የገሊላዋ ቃና ማለት ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስትያን አስተምህሮ በጥምቀት በዓል ማግስት(ጥር 12) ቀን የቃና ዘገሊላ በዓል ይከበራል፡፡ ይህ በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ተያይዞ በድምቀት የሚከበር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዳራ ያለው በዓል ነው፡፡ በዓሉ ቃና ዘገሊላ የሚል ስያሜ ያገኘው ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ሀገር ክፍል በምትሆን ቃና በተባለችው ቦታ በፈፀመው ተአምር መነሻነት ነው፡፡ የቃና ዘገሊላ ጥንተ ነገሩ ወይም ታሪኩ የተፈፀመው የካቲት 23 ቀን ነው፡፡ ነገር ግን አባቶቻችን የውኃን በዓል ከውኃ በዓል ጋር ለማክበር ብለው የየካቲቱን በዓል ወደ ጥር 12 አምጥተውታል፡፡ ይህም ውኃ ወደ ወይን የተለወጠበትን በዓል ከጌታ ጥምቀት በዓል ጋር ለማስተሣሠር ለማስኬድ ነው፡፡ በመሆኑም የቃና ዘገሊላ በዓል ጥር 12 ቀን ይከበራል፡፡
ገሀድ :
➢. ገሃድ የቃሉ ትርጉም መገለጥ መታየት ነው፡፡ በጥምቀት መገለጥ መባሉ ሰው የሆነው አምላክ በዓለም ሲኖር እስከ 30 ዓመት እድሜው ድረስ ሰዎችን ለማዳን የመጣ መሲህ ሰው የሆነበት፣ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ መሆኑን ሳያውቁ ከኖሩ በኃላ በ 30 ዓመት እድሜው በባሕረ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሲጠመቅ አብ በደመና ሆኖ ‹‹የምወደው ልጄ ይህ ነው›› በማለቱ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በራሱ ላይ ሲያርፍ በመታየቱ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ይሰቀላል ይሞታል ይነሳል ብለው የተናገሩለት መሲሕ እርሱ መሆኑ ተገልጦአልና እንዲሁም ሦስቱ አካላት በአንድ ጊዜ ታይተዋልና ምስጢረ ሥላሴ የተገለጠለት በመሆኑ ገሃድ ይባላል፡፡(ማቴ 3፡13-17)