Tuesday, 4 November 2025

ብሔረ ብፁዓን


‎አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን

‎ባሕረ ጥበባት የሆነች ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን አስተምህሮዋ ሙሉ በሙሉ በመለኮታዊ መገለጥ ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ በሥጋዊና በደማዊ የግል አስተሳሰብና ፍልስፍና ላይ የተመሠረተ አንድም አስምህሮ የላትም፡፡ ከልዑል እግዚአብሔር ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት የነበራቸው ልጆቿም ቅድስናን ገንዘብ ያደረጉ ናቸው፡፡ ቅድስናንም ገንዘብ ማድረጋቸው ሰማያዊው ምሥጢር ፍንትው ብሎ እንዲታያቸው ምክንያት ሆኗቸዋል፡፡

‎ፈጣሬ ዓለማት ልዑል እግዚአብሔር አንድ ዓለም ብቻ ሳይሆን 20 የተለያዩ ዓለማትን እንደፈጠረ የምታውቅ ብቸኛዋ የእምነት ተቋም ኦርቶዶክሳዊት ቤተክርስቲያን ብቻ ናት፡፡ ስነ ፍጥረትን እጅግ በሚገርም ሁኔታ ተንትኖ የሚያቀርበው መጽሐፈ አክሲማሮስም ሆነ ሌሎቹ ቤተክርስቲያን ድርሳናት እንደሚያስረዱት ከሆነ እግዚአብሔር 20 የተለያዩ ዓለማትን ፈጥሯል። እነዚህም፡- 5ቱ ዓለማተ መሬት፣ 4ቱ ዓለማተ ማይ፣ 2ቱ ዓለማተ ነፋስ እና 9ኙ ዓለማተ እሳት ናቸው፡፡

Saturday, 1 November 2025

ከፍታህን ምረጥ! ‎

 ‎ 

1. ንስሮች በከፍታ ለብቻቸው ይበራሉ፦ ንስር ፈፅሞ ከጥንብ አንሳ፣ ቁራና መሰል ትናንሽ አእዋፍት ጋር  አብሮ አይበርም።

‎📌 ንስርን በተፈጥሮ ከሚገዳደሩት የወፍ ዝርያዎች መካከል አንዱና ዋነኛ የሆነው ቁራ ነው። ቁራ በንስሩ ጀርባ ላይ በመፈናጠጥ የንስሩን አንገቱን እና ጀርባውን መንከስ ይጀምራል። በዚህን ጊዜ ንስሩ ለመከላከል ወይም ከላዩ ላይ ለማስወገድ የሚያደርገው አንዳችም ዓይነት ምላሽ አይኖርም። ጸብ ውስጥም አይገባም፣ ግጭትም አይፈጥርም።

‎ከቁራው ጋር እየታገለ ምንም ዓይነት ጊዜና ጉልበትንም አያባክንም። ነገር ግን አንድ ነገር ያደርጋል። ይህም ንስሩ ረዣዥም ክንፎቹን በመዘርጋት ከፍ ወዳለው ወደ ሰማየ ሰማያት መወንጨፍ ይጀምራል።

‎ከፍታው በጨመረ ቁጥር ቁራው አየር ንብረቱን መቋቋም ስለማይችል መተንፈስ አስቸጋሪ ይሆንበታል። በስተመጨረሻም በኦክስጂን እጥረት ምክንያት ቁራው ከጀርባው ላይ ይወድቃል። ከራዎች ጋር ጊዜያችሁን አታባክኑ። 

ቀጥታ ወደ ከፍታ ውሰዷቸው። የዚያን ጊዜ መተንፈስ ስለማይችሉ አቅም በማጣት ተሸንፈው ይወድቃሉ። ግያችሁንና ጉልበታችሁን ከደካሞች ጋር በመላፋት አታባክኑ። ከፍታን ምረጡ!!  እናንተ ከፍ ስትሉ ራሳቸው ይወድቃሉ እንጅ እነሱን ለመጣል ምንም ጉልበት አታባክኑ!!!