ኢየሱስ ክርስቶስ፦
ከሦስቱ አካላት አንዱ የሆነ፤ (ማቴ ፳፰፥፲፱)
ከአብ ጋር ዕሪና ያለው፤ (ዮሐ ፲፥፵)
ዓለም ሳይፈጠር የነበረ፤ (ዮሐ ፩፥፩)
ዓለምን የፈጠረ ፈጣሪ፤ (ዕብ ፲፩፥፪)
በቅድምና ከአብ የተወለደ፤ (መዝ ፪፥፯)
ሥጋ እንደሚለብስ በራሱ የመሰከረ፤ (ዘፍ ፫፥፳፪)
ወደ ገነት ገብቶ አዳምን የፈለገ፤ (ዘፍ ፫፥፱)
በነቢያት አስቀድሞ የታወቀ፤ (ኢሳ ፵፪፥፩-፭)
አብ ልጄ ብሎ የጠራው፤ (ማቴ ፲፯፥፭)
ምሳሌ የተመሰለለት፤ (፩ኛ ቆሮ ፲፥፬)
ሱባዔ የተቆጠረለት፤ (ገላ ፬፥፬)
በብሥራተ መልአክ የተጸነሰ፤ (ሉቃ ፩፥፴፩)
ሥጋን የለበሰ (ማቴ ፩፥ ፳፫)
ቁራኝነትን ያጠፋ፤ (፩ኛ ቆሮ ፲፭፥፳፬)

