Sunday, 26 October 2025

ልክ እንደ ቀስት ሁን፡ ወደኋላ መሳብ ረጅም ርቀት ይሄዳል 🏹🌟


በሕይወታችን ውስጥ ነገሮች የዘገዩብን፣ ጊዜያችን የባከነ ወይም ሁኔታዎች ከአቅማችን በላይ ሆነው ወደ ኋላ እየጎተቱን እንደሆነ ተሰምቶን ያውቅ ይሆናል!

ይህ ስሜት ተስፋ አስቆራጭ ቢሆንም፣ ከኋላው ግን የሕይወት ትልቁን ምስጢር ደብቋል።

"አንድ ቀስት ወደ ኋላ በተለጠጠ ቁጥር ወደ ፊት የሚወነጨፍበት ርቀት #እየጨመረ ይሄዳል!"

የእኛም ሕይወትም ልክ እንደዚህ ቀስት ነው። በአሁኑ ጊዜ ከአቅም በላይ በሆኑ ሁኔታዎች ምክንያት ወደ ኋላ የሄድን ወይም ጊዜው የባከነ ቢመስልም፣ ይህ ማለት ግን #አብቅቷል ማለት አይደለም።

Thursday, 23 October 2025

የ666 ሚስጥር እና ከኢሉሚናቲ ሚስጥራዊ ማህበረሰብ በስተጀርባ የተደበቀው እውነት

ምዕራፍ1፡ የ666 እና  የአውሬው ምንነት

📌 የ666 ትርጉም፡-

በመጀመሪያ ደረጃ፣ 666 ቁጥር ከክርስትና መጽሐፍ ቅዱስ የመጣ ነው። የዮሐንስ ራእይ 13:18 "ጥበብ ያለው ሰው አውሬውን ቁጥር ያስብ፤ ቁጥሩ ደግሞ የሰው ቁጥር ነውና፤ ቁጥሩም ስድስት መቶ ስድሳ ስድስት (666) ነው።" በራእዩ ውስጥ፣ "አውሬ" የሚለው ቃል የሐሰት ነቢይ ወይም ፀረ-ክርስቶስ (AntiChrist) ማለት ነው። ስለዚህ 666 የፀረ-ክርስቶስ ምልክት ወይም "ቁጥር" ነው። ይህ ክፉ፣ ከእግዚአብሔር ጋር የሚቃረን ኃይልን ያመለክታል።

ከስሙ ትርጉም ስንነሳ፤ እነዚህ ሦስት ስድስቶች ምንድን ናቸው? በብዙ መልኩ ሊቃውንት አባቶቻችን ቢተረጉሙትም  ለግንዛቤ ያህል ሁለቱን ጠቅሼ አልፋለሁ።

✔ 1ኛ... 666 ማለት፤ የመጀመሪያው 6 የሚወክለው የሰው ልጅ የተፈጠረበትን ቀን ነው። ይህም ስድስተኛው ቀን ነው። ሁለተኛው 6 የሚወክለው የቀትር አጋንንት (ማለትም የአየር ላይ አጋንንት) ከሰማይ ወደ ምድር የተበተኑበትን ሰዓት ይወክላል።  ሦስተኛውና የመጨረሻው 6 ደግሞ የሚወክለው፤ መድሀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት፣ ጠላት ዲያቢሎስ ድል የተነሳበት፣ ነፍሳት ከሲኦል የወጡበት ሰዓት ስለሆነ በዋናነት እነዚህን ሦስት ስድስቶችን የያዙትን ጊዜአት እንደሚቃወም ለመግለፅ ራሱን በሦስት ስድስቶች (666) ወከለ በማለት ሊቃውንት አባቶች ያመሰጥሩታል።

✔ 2ኛ.... 666 ምንድን ነው ለሚለው ደግሞ፤ አባቶቻችን በጥንት መፅሐፍቶች ላይ ከትበውልን እንዳለፉት፤ ሦስት ስድስቶች የሆኑበትን ምክንያት 'ሥላሴን እቃወማለሁ' ማለት ነው ይላሉ። እንዴት ቢሉ፤ ሥላሴ ማለት 'ሠለሰ' ከሚለው የግዕዝ ግስ የወጣ ሲሆን 'ሦስት አደረገ፣ ሦስት' የሚል ትርጉም አለው። የሥላሴ ሦስትነት ምን አይነት ሦስትነት ነው ቢሉ መልሱ ልዩ ሦስትነት ነው። የስድስቶች ብዛት (666) ሦስት የሆነበት ምክንያት አንድም የሥላሴን ልዩ ሦስትነት እቃወማለሁ ሲል ነው ይላሉ።

Saturday, 18 October 2025

ማኅሌተ ጽጌ፤ ምንጩ ትርጉሙና መልእክቱ


ዲ/ን ያረጋል አበጋዝ 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ኃይለ ቃልን ከትርጓሜ፣ ትርጓሜንከምሥጢር እንዲሁም ደግሞ ምሥጢርን ከዜማ ጋርአስተባብረውና አስማምተው የሚደርሱ ሊቃውንት ባለቤትናት፡፡ በ5ኛው መ.ክ.ዘመን የተነሣው ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድአምስቱን ጸዋትወ ዜማ ሲደርስ በ14ኛው መ.ክ.ዘመንየተነሣው አባ ጊዮርጊስ ደግሞ ሰዓታትን ደርሷል፡፡ በዚሁ ዘመንአባ ጊዮርጊስ ጋር ጥልቅ መንፈሳዊ ፍቅር የነበረው አባ ጽጌድንግል “ማኅሌተ ጽጌ” የተባለውን ድርሰት ደርሷል፡፡ ማኅሌተጽጌ ግጥማዊ አካሔድ ያለው ድንቅ ኢትዮጵያዊ ድርሰት ነው፡፡ይህ ድርሰት በማንኛውም ጊዜ የሚጸለይ ቢሆንም በተለየ ሁኔታበቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የሚውለው ከመስከረም 26 እስከኅዳር 5 ቀን ድረስ ባለው የእመቤታችን የቅድስት ድንግልማርያም የስደት ዘመን ነው፡፡ በዚህ ወቅት በየሳምንቱ እሑድሌሊት በሙሉ የእመቤታችንን ከልጇ ጋር ወደ ግብፅ መሰደድናመንከራተት እያሰቡ የሚደረስ ምሥጋናና ጸሎት ነው፡፡

በሀገራችን የመስከረምና የጥቅምት ወራት የአበባ ወራት /ዘመነ ጽጌ/ ናቸው፡፡ ይህም ወቅት ተራሮች በአበባየሚያጌጡበትና ለዓይን ማራኪ የሚሆኑበት ጊዜ ነው፡፡በዚህም ዘመን ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ “ስለልብስስ ስለምን ትጨነቃላችሁ? የሜዳ አበቦች እንዴትእንዲያድጉ ልብ አድርጋችሁ ተመልከቱ፡፡ አይደክሙም፣አይፈትሉም፤ ነገር ግን እላችኋለሁ ሰሎሞንስ እንኳ በክብሩሁሉ ከእነዚህ እንደ አንዱ አልለበሰም፡፡ እግዚአብሔርን ዛሬያለውን ነገም ወደ እቶን የሚጣለውን የሜዳን ሣር እንዲህየሚያለብሰው ከሆነ እናንተ እምነት የጐደላችሁ እናንተንማይልቁን እንዴት እንግዲህ ምን እንበላለን ምንስ እንጠጣለን?ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ ...» /

Saturday, 4 October 2025

ደብረ ደደክን ፍለጋ‼️ ገነት ያለችብት ስፍራ 👉 ከኢትዮጵያ ጀርባ ምን መለኮታዊ ሚስጥር አለ?

 በቲና በቀለ


#ከአመታት_በፊት እንዲህ ሆነ... ከአንድ ወዳጄ ጋር ባህርዳር ጣና አካባቢ ተቀምጠን በብዙ ሀሳቦች ላይ እየተወያየን ባለንበት ሰአት እኛ ከተቀመጥንበት በስተቀኝ በኩል ጓደኛዬ የሆኑ የውጭ ሀገር ዜጎችን ይመለከታል እንዳስታውላቸው ይነግረኛል።

ሴትና ወንድ በእድሜም ጠና ያሉ ነጮች ናቸው፤ ወደ ሰሜን ምዕራብ ጣና ሀይቅ አካባቢ ውድ፣ ዘመናዊ በግለሰብ ደረጃ ብዙም የማይገኘው መቅረጸ ትዕይንት Camera አቅርቦ የሚያሳይ telescope ከጀረባቸው እንዲሁም ትልቅዬ ቦርሳን አዝለው ወደ ሀይቁ አይናቸውን በሁለት አቅጣጫ እያመላለሱ በተደጋጋሚ ይመለከታሉ።


ለብዙ ደቂቃወች ይህንን የጠለቀ እይታ እና የሚጠቀሙትን ውድ ዘመናዊ Telescope ስመለከት እኒህ ሰው የመልካ ምድር አሳሾች ወይም የጥንት መዛግብት ተመራማሪወች ሊሆኑ እንደሚችሉ ገመትኩ።......